አዲሱ የዲጂታል ዘመን ሥልጣኔ በኢትዮጵያ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቀደም ባሉት ዓመታት አንድ የመንግሥት አገልግሎት ለማግኘት፣ መታወቂያ ለማደስ ወይም የንግድ ፈቃድ ለማውጣት ይደርስ የነበረው እንግልት የብዙዎቻችን የዕለት ተዕለት ትዝታ ነበር። ረጅም ሰልፍ፣ «ዛሬ ኃላፊው የሉም» የሚል ምላሽ እና የፋይል ተፈልጎ አለመገኘት የህብረተሰቡ የዘወትር ምሬት ነበሩ። ዛሬ ግን ያ ታሪክ በከፍተኛ…
ለመዲናችን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት በቅንነትና በታማኝነት እየሰራን እንገኛለን – ከንቲባ አዳነች አቤቤ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለመዲናችን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት በቅንነትና በታማኝነት እየሰራን እንገኛለን አሉ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፡፡ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ አራት ዘመናዊ የተሽከርካሪ ማቆሚያዎች፣ ተርሚናሎችና ገበያ ማዕከላት (በጎተራ፥ ቦሌ፣ የካ እና ቀበና) መርቀው በዛሬው ዕለት አገልግሎት አስጀምረዋል። ከንቲባ አዳነች…
በሆርሙዝ ሰርጥ የተቀበሩ ፈንጂዎችን አጽድተናል – ፕሬዚዳንት ትራምፕ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን መንግሥት በሆርሙዝ ሰርጥ የቀበራቸውን ፈንጂዎች ሙሉ በሙሉ አጽድተናል አሉ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ። በዓለም ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባለው የሆርሙዝ ሰርጥ ዙሪያ እንደ አዲስ ውጥረት መንገሡ ተሰምቷል። ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ባካሄደችው ፈጣን ዘመቻ፣ ዓለም አቀፍ የውኃ ክልል በሆነው…
የኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ የሽግግር ጉዞ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአንድ ሀገር ዘላቂና ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚረጋገጠው ጤናማና አምራች ማኅበረሰብ መፍጠር ሲቻል ነው። የጤና አገልግሎትን በጥራትና በስፋት ተደራሽ ማድረግ ደግሞ ጤናማና አምራች ማኅበረሰብን ለመገንባት መሠረታዊ ቅድመ ሁኔታ ነው። በታዋቂው የታሪክ ተመራማሪ ዩቫል ኖአህ ሐራሪ “ሆሞ ዴውስ” በተሰኘው መጽሐፋቸው…
በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 2ኛውን ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበችው ተማሪ – ሕዳሴ ዘመኑ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን እንጅባራ ከተማ የሚገኘው የአገው ምድር 2ኛ ከፍተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዋ ሕዳሴ ዘመኑ በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና 583 በማምጣት 2ኛውን ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች፡፡ በስሟ ቤተ መጽሐፍት የተሰየመላት ጀግናዋ ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑ በተፈጥሮ ሳይንስ በሀገር አቀፍ ደረጃ 2ኛውን…
ለዘመናት በስኬት የዘለቀው የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ በስኬት የታጀበ የውጭ ግንኙነት ታሪክ ያላት ሀገር ናት፡፡ ከቀደሙት ነገስታት ጀምሮ በቅርብም ሆነ ሩቅ ካሉ የዓለም ሀገራት እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ጠንካራ የውጭ ግንኙነቶችን መስርታ ብሔራዊ ጥቅሞቿን እያስጠበቀች እስከ ዛሬ ዘልቃለች፡፡ እ.ኤ አ በ1920ዎቹ አፍሪካውያን እህት ወንድሞቻችን…
በሁሉም አማራጮች የአህጉሪቱን የጤና ሉዓላዊነት ማረጋገጥ ይገባል – መሐሙድ አሊ ዩሱፍ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሁሉንም አማራጮች በመጠቀም የአህጉሪቱን የጤና ሉዓላዊነት ማረጋገጥ ቀጣይነት ያለው ተግባር ሊሆን ይገባል አሉ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር መሐሙድ አሊ ዩሱፍ፡፡ በአምስት የጤና ዘርፍ ምሰሶዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ለአራት ቀናት የሚቆየው 76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ…
ቃልን በተግባር↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19 ፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በመገጭ ግድብ ላይ ነፍስ የዘራው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ውሳኔ የመደመር መንግሥት ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ባለፈ በተያዘላቸው ጊዜና በሚፈለገው ጥራት ስለማጠናቀቁ ምስክር ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ከአማራ ክልል የልማት ጥያቄዎች መካከል…
የለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ላይ እያየን ያለው ለውጥ ከሁሉ የሚልቅ ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በከተማችን ላይ ከሚታየው ለውጥ ሁሉ የሚልቀው የለነገዋ የሴቶች የተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል ላይ እያየን ያለው ለውጥ ነው አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ። ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ፥ ዛሬ የልጆች ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (CIFF) መስራች እና የቦርድ ሃላፊ ክሪስ ሆን እና ቡድናቸውን ለነገዋ የሴቶች…
የ12 ኛ ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ስዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)የ12 ክፍል ተፈታኞች ውጤታቸውን ዛሬ ከምሽቱ 1 ስዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ አለ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት። የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርቲፊኬት ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆኗል። በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት…
የሀገር ግንባታ ውል የተቋጠረበት ምርጫ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሀገራት የልማት ጉዞ ጠንካራ ተቋማትን፣ የሕዝብ ተሳትፎንና የዴሞክራሲ ባህልን መገንባት የሚጠይቅ እንደመሆኑ ኢትዮጵያ ያከናወነችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የእድገት ጉዞዋ ጉልህ ምዕራፍ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት ብትሆንም፤ በአንጻሩ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ በማካሄድና በሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ረገድ…
ከፅንሰ-ሃሳብ እስከ አህጉራዊ የመሪነት ሚና:- ዲጂታል ኢትዮጵያ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መረጃ በከፍተኛ ፍጥነት በሚበራከትበትና ዓለም በቴክኖሎጂ ወደ አንዲት መንደር በተቀየረችበት በዚህ ዘመን፣ ፍጥነትና የቴክኖሎጂ ዝግጁነት የብሔራዊ ህልውና እና የዕድገት መለኪያ ሆነዋል። ይህን የዘመኑን እውነታ ቀድማ የተረዳችው ኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞዋን ለራሷ ሃገራዊ ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካም አርአያ…
የደባርቅ ከተማን የቱሪስት መዳረሻነት ለማጠናከር ሁሉም የበኩሉን ሚና ሊወጣ ይገባል – ፕሬዚዳንት ታዬ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ መግቢያ በር የሆነችውን ደባርቅ ከተማ ለማዘመንና ለቱሪዝም ምቹ ለማድረግ ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በመርሐ ግብሩ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና ሌሎች…
በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያመጣው ተማሪ…ጃላል ግርማ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ልዩ አዳሪ ት/ቤት ተማሪ የሆነው ጃላል ግርማ ኩሳ በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ማጠናቀቂያ ፈተና 591 ነጥብ 6 በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል፡፡ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስ ከ600 አጠቃላይ ውጤት ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበው በአዳማ…
ኢትዮጵያ የ2028ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ ለካፍ ጥያቄ አቀረበች↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የ2028ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለማስተናገድ ጥያቄዋን ያቀረበችበትን ሰነድ ለአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) አስገብታለች፡፡ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከኢፌዴሪ መንግሥት ጋር በጋራ አስፈላጊ ሰነዶችን ያካተተ ዶክመንት ለካፍ ማስገባቱን አስታውቋል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ ትልቁን አህጉራዊ የእግር ኳስ ድግስ ለ4ኛ…
የመውሊድ በዓልን ምክንያት በማድረግ 9 ጊዜ መድፍ ይተኮሳል↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በነገው ዕለት የሚከበረውን 1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) ምክንያት በማድረግ ዘጠኝ ጊዜ መድፍ ይተኮሳል አለ መከላከያ ሚኒስቴር፡፡ መድፉ ነገ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12 ሰዓት ላይ እንደሚተኮስ በሚኒስቴሩ የመከላከያ ስፖርትና ኪነ ጥበባት ሥራዎች ማዕከል ለፋና ዲጂታል…
ዘመኑን ያልዋጀው የካይሮ የቅኝ ግዛት መነፅር↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሰሞነኛው ከካይሮ የሚሰሙት ተደጋጋሚ እና መሠረተ ቢስ ውንጀላዎች የኖረውንና ያረጀውን የፖለቲካ ትርክት እንደገና ለማደስ የሚደረጉ የከንቱ ጥረቶች ማሳያ ናቸው። ግብፅ አሁንም ድረስ የታላቁን የዓባይ ወንዝ ተፈጥሯዊና ሕጋዊ ፍሰት እንደ ግል ሐይቋ አድርጋ ለመመልከት የምትሞክርበት መነፅር፣ በ21ኛው ክፍለ ዘመን የማይሠራ፣ በቅኝ…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡- እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ…
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1 ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ከንቲባዋ በመልዕክታቸው፥ በዓሉን እንደከዚህ ቀደሙ የተቸገሩትን በመርዳት፣ ለሌላቸው በማካፈልና የታረዙትን በማልበስ እንዲሁም…
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ያስተላለፈው መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም ለሚገኙ የእስልምና እምነት…
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያስተላለፈው መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡- በሀገራችንና በመላው ዓለም ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1ሺህ 501ኛው የነቢዩ መሐመድ…
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ (ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡ እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የልደት በዓል (መውሊድ) አደረሳችሁ! መውሊድ…
የኢትዮጵያውያን የውይይት ድልና የከሰሩት ታሪካዊ ጠላቶች↗
የሀገር ሕመም የገዘፈው፣ ስብራቱም የሰፋው ታሪካዊ ጠላቶች በከፈቱት አሉባልታና ሴራ ብቻ አልነበረም፤ ይልቁንም የገዛ ልጆቿ የሀሳብ መድረክ አጥተው፣ እርስ በርስ መደማመጥ ተስኗቸው በየጎጇቸው በገነቡት የእኔነት አጥር ጭምር እንጂ። የሕብራዊነት ማሕደር፣ የባሕልና የታሪክ እልፍኝ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ ዛሬ ግን የዘመናት የፖለቲካ ስብራቷን የምትጠግንበት አዲስና ስልጡን ጥበብ…
ሊቨርፑልና ኒውካስል ዩናይትድ አቻ ተለያዩ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ሊቨርፑልና ኒውካስል ዩናይትድ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ የኒውካስልን ግቦች አንቶኒ ኢላንጋና ጆሴፍ ዊሎክ ሲያስቆጥሩ ÷ የሊቨርፑልን የአቻነት ግቦች ደግሞ ኮዲ ጋክፖና ዶምኒክ ስቦዝላይ ከመረብ አሳርፈዋል። The post ሊቨርፑልና ኒውካስል ዩናይትድ አቻ ተለያዩ…
“ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ሌሎች ሀገራት በሚያዩን ልኬታና ከፍታ እራሳችንን እንድንመለከት እማጸናለሁ” – ፕሬዚዳንት ታዬ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ሌሎች ሀገራት በሚያዩን ልኬታና ከፍታ እራሳችንን እንድንመለከት እማጸናለሁ ሲሉ መላ ኢትዮጵያውያንን ጠይቀዋል፡፡ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የሀገራዊ ምክክር ጉባዔ ማጠቃለያ ሥነ ሥርዓት በትናንትናው ዕለት ተካሂዷል፡፡ ፕሬዚዳንት ታዬ በመርሐ ግብሩ ላይ…
ማንቼስተር ሲቲ በርንማውዝን 2 ለ 1 አሸነፈ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በርንማውዝን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በአዲስ አሰልጣኝ የተመራው ማንቼስተር ሲቲ በርንማውዝን በማሸነፍ በሊጉ መርሐ ግብር የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል፡፡ ማርከስ ታቨርኔር በርንማውዝን በ26ኛው ደቂቃ ቀዳሚ ያደረገ ቢሆንም ማርክ ጉሂ በ85 እና…
ኢትዮጵያ ቱሪዝም ስትራቴጂክ የብሪክስ ትብብር መስክ እንዲሆን ጥሪ አቀረበች↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ያሏትን የቱሪዝም እና የስፖርት ፀጋዎች ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ስትራቴጂካዊ ጥሪ በብሪክስ መድረክ ላይ አቅርባለች፡፡ ኢትዮጵያ በህንድ ጃይፑር በተካሄደው የቱሪዝም ሚኒስትሮች ስብሰባ እና በስፖርት ሚኒስትሮች ጉባኤ ላይ በመገኘት፣ አባል ሀገራቱ በተጨባጭ ተግባራት ላይ ያተኮረ ትብብር…
የኢትዮጵያ እናትነት በኡሁሩ ኬንያታ አንደበት↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የፓን አፍሪካኒዝም ምሳሌ፣ የነጻነት ምልክት እና የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በመሆን የአፍሪካ እናትነቷን በተግባር ያሳየች ሀገር ናት፡፡ ይህ እውነት ከኢትዮጵያውያን ባለፈ በተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ፖለቲከኞች እና የታሪክ ተመራማሪዎች እውቅና ሲያገኝ ደግሞ የኢትዮጵያን አህጉራዊ መሪነት ሚና ይበልጥ ያጠናክረዋል፡፡…
የባሕር በር ተጠቃሚነት ለቀጣናዊ ኢኮኖሚ እድገት↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የባሕር በር ተጠቃሚ መሆን ከኢኮኖሚ፣ ከንግድ፣ ከደህንነት እና ከዓለም አቀፍ ግንኙነት አንፃር እጅግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል፡፡ የባሕር በር ባለቤትነትን ማረጋገጥ በዓለም አቀፍ ፖለቲካ እና ጂኦፖለቲካዊ ግንኙነት ውስጥ በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም። በታሪክ አጋጣሚዎች እንደተስተዋለው የባሕር በር ባለቤት የሆኑ ሀገራት ከኢኮኖሚ…
ዮሚፍ ቀጀልቻ የግማሽ ማራቶን ክበረ ወሰንን ሰበረ↗
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በአርጀንቲና የተካሄደውን የቦነስ አይረስ ግማሽ ማራቶን ውድድር አሸንፏል፡፡ አትሌት ዮሚፍ ርቀቱን 56 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በሆነ ጊዜ በማጠናቀቅ ነው የግማሽ ማራቶን የዓለም ክብረ ወሰንን ዳግም ማሻሻል የቻለው፡፡ ዮሚፍ ኡጋንዳዊው ጃኮብ ኪፕሊሞ በሊዝበን ያስመዘገበውን የ57 ደቂቃ ከ20 ሰከንድ የቀድሞ…