የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት ጉልህ አበርክቶ አለው – አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ የተቀረጹት ዘርፎች ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ዕድገት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው አሉ የኢኮኖሚ ባለሙያው አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ፡፡ አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ፥ ዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት ባወጣው የቅርብ ጊዜ መረጃ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ከተመዘገበባቸው ጥቂት ሀገራት…
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ 7 ጨዋታዎች ይደረጋሉ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በአራተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት 7 ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዚህም ምሽት 4 ሰዓት ላይ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡ በሊጉ እስካሁን ድረስ ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈው አርሰናል ተከታታይ 4ኛ ድሉን ለማሳካት ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡ ባለሜዳው…
18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባዔ በሕንድ ኒው ዴልሂ መካሄድ ጀመረ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) 18ኛው የብሪክስ መሪዎች ጉባዔ በሕንድ ኒው ዴልሂ መካሄድ ጀምሯል። በጉባዔው ላይ የብሪክስ አባል እና አጋር ሀገራት መሪዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሚሳተፉ ይሆናል። የብሪክስ አባል ሀገር የሆነችው ኢትዮጵያም በጉባዔው ላይ ተሳትፎ እያደረገች ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)…
የኢትዮጵያ የማንሠራራት ዘመን አዲስ ምዕራፍ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ለዘመናት ስለ ኢትዮጵያ የሚጻፉ የታሪክ መዛግብት ሀገሪቱን ተቃርኖ በሞላበት ትርክት ይገልጿት ነበር። “የምሥራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ” እየተባለች በምድረ-በዳ ጥም የምትቃጠል፤ “የዓባይ ወንዝ ዋና ምንጭ” ሆና ሳለች በጨለማ የምትማቅቅ ሀገር ተብላም ትታወቅ ነበር። ከዓባይ ውሃ 86 በመቶውን የምታበረክተው ኢትዮጵያ፣ ሃብቷን…
ለቃል ታምኖ በተግባር መጽናት፤ የመደመር መንግሥት መገለጫ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያውያን ዘንድ ለቃል ትልቅ ቦታ ይሰጣል፤ ስነ ቃሎች ሳይቀር ለቃል የምሰጠውን ቦታ የሚሳዩ ናቸው፡፡ የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ ይባላል፤ ለቃል ምን ያህል ቦታ እንደምንሰጥ ከዚህ የላቀ ማሳያ አይኖርም፡፡ የትናንት ተግባር ለዛሬ ምስክርነት የሚቆም በመሆኑ የለውጡ መንግሥት ባለፉት ዓመታት ያስመዘገባቸው ስኬቶች…
ህንድ እና ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ወዳጅነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ዘርፎች እያሸጋገሩ ነው – የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ህንድ እና ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ወዳጅነታቸውን ወደ አዲስ የትብብር ዘርፎች እያሸጋገሩ ነው አሉ የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፡፡ የህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ18ኛው የብሪክስ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ…
ኢትዮጵያና ሕንድ ጥልቅ ታሪካዊ ትስስርና የዘመናት የባህል ግንኙነት አላቸው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያና ሕንድ ጥልቅ ታሪካዊ ትስስርና የዘመናት የባህል ግንኙነት አላቸው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከብሪክስ የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የኢትዮጵያ ሕንድ አጋርነትን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት…
ኢትዮጵያ፤ ፈተናን ወደ ዕድል ቀይራ ወደ ከፍታ የምትጓዝ ሀገር↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) የአንድ ሀገር እውነተኛ አቅም የሚለካው በተመቻቸ ሁኔታ ውስጥ በሚታለም ህልም ሳይሆን፤ በፈተናዎች መካከል ተስፋን ሰንቆ የዕድል መንገዶችን በመጥረግ በሚደረግ የጽናት ጉዞ ነው። የታሪክና የጽናት ምድር የሆነችው ኢትዮጵያም በተደራራቢ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊና የልማት ፈተናዎች ማዕበል ውስጥ አልፋ፤ የመዋቅራዊና የዘርፍ…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያዩ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከብሪክስ ጉባዔ ጎን ለጎን ከሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለቱን ሀገራት አጋርነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በ18ኛው የብሪክስ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ሕንድ ገቡ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 2፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ18ኛው የብሪክስ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ኒው ዴልሂ ሕንድ ገብተዋል። ጉባዔው “ጽናትን፣ ፈጠራን፣ ትብብርን እና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የሚካሄደው፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የተመራው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ከጉባዔው ጎን ለጎን ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ…
በ18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ የአባል ሀገራቱ መሪዎች ኒው ዴልሂ እየገቡ ነው↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) 18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ በነገው ዕለት በሕንድ መዲና ኒው ዴልሂ መካሄድ ይጀመራል። በ18ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ የአባል ሀገራቱ መሪዎች ወደ ከተማዋ እየገቡ ይገኛል፡፡ ከጉባኤው አስቀድሞ በሕንድ ንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር አዘጋጅነት የብሪክስ የንግድ መድረክ በዛሬው ዕለት የተካሄደ ሲሆን…
ታራሚዎች በምህረት የተፈቱት የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት በፍቅር ለመጀመር ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በመቶ የሚቆጠሩ ታራሚዎች በምህረት የተፈቱት የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት በፍቅር፣ በይቅርታ እና በሰላም ለመጀመር ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ2019 አዲስ ዓመትን አስመልክተው ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት÷ ሀገራዊ ምክክራችን ገደ መልካም መሆኑን በምክክሩ ብቻ ሳይሆን…
ከድሮን ትዕይንትነት ባሻገር↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲሱ ዓመት ዋዜማ የአዲስ አበባ ሰማይ በአስደናቂ የድሮን እና የርችት ትዕይንት ደምቆ አድሯል። በመዲናዋ በተካሄደው ልዩ የአዲስ ዓመት አቀባበል 3 ሺህ ድሮኖች ሰማዩን በኅብረ ቀለም በማስጌጥ የሀገሪቱን ታሪክ፣ ልማት እና የተስፋ መንገድ የሚያሳይ በአየር ላይ የተሳለ ምስል በድንቅ ቅንጅት አስመልክተዋል። ይህ በአፍሪካ…
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካ አንድነት ኃይል ነው – ታይም አፍሪካ መፅሔት↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጄክት ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ አንድነት ኃይል ነው አለ የታይም አፍሪካ መፅሔት፡፡ መፅሔቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አስመልከቶ ባወጣው ሀተታ÷ ግድቡ በዘመናችን ካሉ ታላላቅ የአፍሪካ ታሪኮች አንዱ እና የአፍሪካውያን የጋራ ሀብት መሆኑን ጠቅሷል፡፡ በአባይ ወንዝ ላይ…
በ3 ሺህ ድሮኖች የደመቀው የዋዜማ ምሽት፡ በራስ አቅም ወደ ቴክኖሎጂ ከፍታ↗
ዘመኑ የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ውድድር የገነነበት ነው። ሀገራት ከሰለጠነ የሰው ኃይል ባለቤትነት እስከ ዲጂታል ሽግግር አዳዲስ ከፍታዎችን ለመቆናጠጥ በእሽቅድድም ላይ ናቸው፡፡ በዚህ ዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታ ውስጥ ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት እሳቤ በቴክኖሎጂው መስክ እያመጣች ያለችው ለውጥ እና እያስመዘገበችው ያለው ድል አበረታች ነው፡፡ በተለይም በራስ…
የተሳለጠ ሎጂስቲክስ ግዙፍ ኢኮኖሚና ብዙ ሕዝብ ላላት ኢትዮጵያ ወሳኝ ሚና አለው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘመኑን የዋጀ ሎጂስቲክስ ግዙፍ ኢኮኖሚ እና ብዙ ሕዝብ ላላት ኢትዮጵያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የሞጆ ሎጂስቲክስ ማዕከል ምረቃ ላይ ባደረጉት ንግግር ÷ ሎጂስቲክስ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ እድገት ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ገልፀዋል፡፡…
የአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግሥት ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግሥት ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ፣ የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ለኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕዝብ የሰላም ምኞታቸውን ገልጸዋል።…
ብርሃናማው ቀን መስረከም አንድ↗
አዲስ አበባ፣ መስከረም 1፣ 2019 (ኤፍ ኤም ሲ) ዛሬ መስከረም አንድ ነው፡፡ አንድ የምንለው ግን ለቀን መቁጠሪያ ብቻ አይደለም፤ ለአዲስ ጅምር ለአዲስ ተስፋ ለአዲስ ስኬትም ነው። ዛሬ በሀገራችን አራቱም ማዕዘን የደስታና የአዲስ ተስፋ ስሜት ሰፍኗል፤ ህዝቡ በባህል አልባሳት አጊጧል፤ መስኩ አደይ አበባ ለብሷል። ማለዳ በየሰፈሩ የእንቁጣጣሽ ተናፋቂ ዜማ ይሰማል በለመለመ…
ዕድል ማግኘት፡ የዲጂታል ኢትዮጵያ ተጨባጭ ማሳያዎች↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት “እርሷ አልተቀየረችም፤ የተቀየረው ዕድል ማግኘቷ ነው” ሲሉ በዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ውስጥ የአንዲት ሴት ነጋዴን የዲጂታል ጉዞ ሽግግር የሚያሳይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ቴክኖሎጂና ምቹ ሁኔታዎች ሲፈጠሩ በእያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት ውስጥ የሚመጣውን…
የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ ዐሻራ 8 ነጥብ 2 ቢሊየን ችግኞችን በመትከል በስኬት ተጠናቅቋል – አቶ አዲሱ አረጋ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 ዓ.ም (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር 8 ነጥብ 2 ቢሊየን ችግኞችን በመትከል በስኬት ተጠናቅቋል አሉ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ፡፡ አቶ አዲሱ አረጋ የመርሐ ግብሩን መጠናቀቅ አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፥ የ2018 የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር 8 ቢሊየን ቸግኞችን እንደ ሀገር ለመትከል ታቅዶ በከፍተኛ…
አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። አፈ ጉባዔው በመልዕክታቸው÷ የተፈጥሮ ዑደት የሆነው የዘመን መለወጥ ሰዎች ከትናንት እንዲማሩ እና ነገን በተስፋ ለመገንባት አዲስ ጉዞ እንዲጀምሩ የሚያደርግ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በብዝኀ ቋንቋዎች፣…
ለኮንፍረንስ ቱሪዝም ተመራጭ የሆነችው አዳማ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አዳማ ከተማ በዘመናዊ የከተማ ልማት ውበትና በተፈጥሮ በረከት ያጌጠች ንቁ የኢኮኖሚና የባሕል ማዕከል ናት። ከተማዋ ካሏት በርካታ መገለጫዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰውና በፍጥነት እያደገ የመጣው የኮንፍረንስ ቱሪዝም ዘርፍ አንዱ ነው። አዳማ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ስብሰባዎችን፣ ኤግዚቢሽኖችንና…
የኢትዮጵያ የዘመን መጽሐፍ ካሁን በኋላ የጠብመንጃና የጉልበት ታሪክን አይመዘግብም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 ዓ.ም (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ የዘመን መጽሐፍ ካሁን በኋላ የጠብመንጃና የጉልበት ታሪክን አይመዘግብም አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ÷ ሀገራዊ ምክክሩ ገደ መልካም መሆኑን በምክክሩ ብቻ ሳይሆን በውጤቱም እያሳየ ነው…
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በመልዕክታቸው እግዚአብሔር…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለአዲሱ ዓመት ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፡-↗
ዘመን ከፈጣሪ ለሰው የተሰጠ መሥሪያ መጽሐፍ ሲሆን፣ ለእያንዳንዱ ሰው የተሰጡ የተወሰኑ ገጾች አሉት። የመጨረሻው ገጽ እስኪከደን ድረስ የፈለግነውን የመጻፍ መብት በእጃችን ይገኛል። የትናንቱ ዘመን ጠባሳውንም ዐሻራውንም፣ ዕዳውን ምንዳውንም ሰጥቶን አልፏል። አሁን ወሳኙ ነገር በቀሩን ዘመናት ምን ቁም ነገር እንሰራለን? የሚለው ነው። ኢትዮጵያውያን ዛሬ ለትውልድ የሚተርፍ…
አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ ከ600 በላይ እስረኞች ከእስር ተፈቱ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 ዓ.ም (ኤፍ ኤም ሲ) አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር ተፈትተዋል፡፡ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል ለመናድ ሞክረዋል በሚል ታስረው የነበሩ ግለሰቦች እንዲፈቱ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከመንግስት ጋር ላለፉት 5 ወራት ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል። በፍርድ ቤት ውሳኔ…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡ እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! ዘመን ከፈጣሪ ለሰው የተሰጠ የመሥሪያ መጽሐፍ ነው። ይህ የመሥሪያ መጽሐፍ ለእያንዳንዱ ሰው…
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስተላለፉት መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡ The post ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለአዲሱ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ appeared first on…
አዋሽ ባንክ በአበባየሆሽ / ሽኖዬ ቲክቶክ ውድድር የ2 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር ሽልማት አዘጋጀ↗
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አዋሽ ባንክ መጪውን የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ የ2 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የአበባየሆሽ / ሽኖዬ የቲክቶክ ቻሌንጅ ሽልማት ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ ተወዳዳሪዎች በአበባየሆሽ ወይም ሽኖዬ ግጥም በማዘጋጀትና የፈጠራ ጥበብን በማሳየት እስከ 1 ሚሊየን ብር መሸለም ይችላሉ፡፡ ስለሆነም ተወዳዳሪዎች ከዚህ በታች…
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት መሰረታዊ የሸቀጦችን የገበያ ዋጋ ለማረጋጋት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው↗
አዲስ አበባ፣ጳጉሜን 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘጠና ዓመት የንግድ ሥራ ልምድ ያለው የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት አዲሱን የ2019 የዘመን መለወጫ እና መጪ በዓላትን ምክንያት በማድረግ የሸቀጦችን ዋጋ ለማረጋጋትና የአቅርቦት ክፍተቶችን ለመሙላት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው፡፡ ድርጅቱ የደንበኞቹን ፍላጎት መሠረት በማድረግ በተለይም መሠረታዊ የምግብ እና…